ህብረ ብሔራዊ የእህትማማችነት እሴትን በማዳበር የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት ይጠበቃል፦ አቶ ግርማ ባሻ

Spread the love

‎ህብረ ብሔራዊ የእህትማማችነት እሴትን በማዳበር የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት ይጠበቃል ሲሉ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግርማ ባሻ ገለጹ

‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሴቶች ፌደሬሽን አንደኛ መደበኛ ጉባኤ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው

‎በጉባኤው የ2017 የእስካሁን ሥራዎች ሪፖርት መገምገም፣ አመራሮችን መልሶ ማደራጀት፣በፌደራል የሴቶች ፌድሬሽን ሶስተኛ መበደኛ ጉባኤ ክልሉን ወክለው የሚሳተፉ አባላትን የተጓደለ በማሟላት እወቅና መስጠት ፣የፌድሬሽኑን አደረጃጀቶች ለማጠናከር ስልጠናዎች ይስጣል።

‎የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግርማ ባሻ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ፌድሬሽኑ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ሊያረጋግጡ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።

‎ሴቶችን በማህበራዊ ልማትና ኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ከባለድርሻ አካላት ጋር በተናበበና በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

‎የዲሞክራሲ እሴቶችን በማዳበር ሴቶች በሀገረ መንግስት ግንባታ ላይ እያተደረጉት ያለውን ዘርፈ ብዙ ጥረቶች ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

‎የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሪት ለምለም አምሳሉ በበኩላቸው ቢሮው የተለያዩ አደረጃጀቶችንና የአሰራር ስርዓቶችን በማጠናከር የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ተልዕኮውን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

‎ፌደሬሽኑ እስካሁን ባለው በተቀናጀ ጥረት እያከናወነ ያለውን ዘርፈ ብዙ ስኬቶችን አጠናከሮ በማስቀጠል በድክመት የታዩትን ጉዳዮች ፈጥኖ በማረም ጠንካራ ፌድሬሽን ሊኖር እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

‎የክልሉ የሴቶች ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ትዕግስት ወርቁ በፌደሬሽኑ እስካሁን እየተከናወኑ ያሉትን ሥራዎች ሪፖርት እያቀረቡ ይገኛል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *