




ወጣቶች የብሔራዊነት ገዥ ትርክትን በሕዝብ ዘንድ የማስረጽና የማጽናት መሠረት እንዲያዝ የሚያስችሉ ሥራዎችን በትኩረት መስራት እንደሚገባ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ ገለጹ።
የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ለወጣቶች እየሰጠ ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ ዛሬም እንደቀጠለ ነው።
በስልጠናው የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ እንደገለጹት ወጣቱ ትውልድ የብሔራዊነት ትርክትን ምንነትና የግንባታ ሂደቶቸን በአግባቡ ተረድተው ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ማስቻልን ዓለማ ያደረገ ነው።
ብልጽግና ፓርቲ በሀገራችን ፖለቲካዊ ስብራቶች የተነሳ ከወረሳቸው ውርስ ዕዳዎች ውስጥ ዋነኛው ገዥ ሀገራዊ ትርክት አለመገንባቱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዚህም ፓርቲው የፖለቲካ ስብራቶችን ለመጠገን አዲስ ሁሉንም የሀገራችን ህዝቦች የሚያሰባስብ ፣አካታች፣ለሁሉም ማንነቶች አመች የሆነ ገዥ ሀገራዊ ትርክት ለመገንባት በርካታ ስራዎችን እየተሰራ ይገኛል።
ጽንፍ የያዙ ትርክቶች በጋራ የወደቅንባቸው አክሳሪ ትርክቶች መሆኑን የገለጹት አቶ ነጋ እነዚህ ትርክቶች ጉድለቶች የብሔራዊነት ገዥ ትርክት እንዲፈጠር ገፊ ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
ከፋፋይ እና አሉታዊ ትርክቶችን የመከላከል ሥራ ምሉዕነት የሚኖረው የህብረ ብሔራዊነትን ማዕከል ያደረገ የብሔራዊነት ትርክትን በሚገባ በማስረጽ ጽኑ መሠረት ማስያዝ ስቻል ነው።
በዚህም ወጣቶች የብሔራዊነት ገዥ ትርክት የበላይነቱን እንዲይዝ የጋራ ትናቶችን፣ዛሬን እና የጋራ ነገያችን ላይ በትኩረት በመስራት የጀመርነውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ጉዞ እውን እንዲሆን ብርቱ ትግል ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።
ጠንካራ ማህበራዊ መስተጋብር መፍጠር ፣ጠንካራ ኢኮኖሚ እና ፖለቲካ አቅም በመገንባት ሁሉን አሰባሳቢ የገዥ ትርክት ግንባታን ለማፋጠን ወጣቶች በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቃል ብለዋል።
የሕዝቦችን አብሮነትና አንድነት በማጠናከር፣ ወንድማማችነትና አህትማማችነት እሴቶችን ይበልጥ በማጎልበት የጋራ አስተሳሳሪ ትርክትን አጠናክሮ በማስቀጠል የጋራ ሀገር፣የጋራ ብልጽግና ለመገንባት በቁርጠኝነት መስራትን ይጠይቃል ብለዋል።
ወጣቱ ከምንም ጊዜ በላይ አፍራሽ ትርክቶችን በማረም የአርበኝነት ስሜትን በመላበስ የብሔራዊነት ገዥ ትርክት ጎልቶ እንዲወጣ ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
