




የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ስራ አመራር ቦርድ ውይይት በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በውይይቱ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ፍቅሬ አማን ሚዲያው በተደራጀ መንገድ አየር ላይ እንዲወጣ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ፍቅሬ አክለውም ክልሉ የሚዲያ ተቋም አስፈላጊነት በመገንዘብ በሰጠው ትኩረት ክልሉ የራሱ ሚዲያ በማደራጀት በዌብሳይትና በማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።
ሚዲያው የህብረተሰቡን የመረጃ ተደራሽነት ከማረጋገጥ ባሻገር የክልሉን እምቅ ፀጋ በመግለጥ ረገድ የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ቦርዱ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ያደርጋል ብለዋል።
በመድረኩ የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የ2017 ዓ.ም አፈፃፀም በሚዲያ ኔትወርኩ ዋና ስራ አስኪያጅ ቀርቧል።
አቶ መንግስቱ ባቀረቡት ሪፖርት ተቋሙ ከተደራጀ ወዲህ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመው አሁን ላይ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስራዎችን ለማስጀመር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
እንዲሁም የሚዲያ ተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ በሚዲያ ኔትወርኩ ምክትል ስራ አስኪያጅና ይዘት ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር ካሳሁን ወዳጆ ቀርቦ የሚጸድቅ ይሆናል።
ስራ አመራር ቦርዱ የተቋሙን የ2017 አፈፃፀምና የ2018 ዕቅድ፤ የቴሌቪዥንና የስቱዲዮ ግንባታ ሂደት፤ የሚዲያውን ኢዲቶሪያል ፖሊስን ጨምሮ የተለያዩ መመሪያዎችን መርምሮ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል ሲል ደብብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።
