በቤንች ሸኮ ዞን በአጠቃላይ 134 አመራሮችን ከኃላፊነት የማንሳት ፣ የማሸጋሸግና በአዲስ መልክ የማደራጀት ስራ ተሰርቷል ፦ አቶ ደግፌ ኩድን

Spread the love

በቤንች ሸኮ ዞን በተካሄደ የአመራር ምዘናና ግምገማ፣ 134 አመራሮችን ከኃላፊነት የማንሳት፣ የማሸጋሸግና በአዲስ የመመደብ ሥራ መከናወኑን የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ ኩድን አስታወቁ።

እንደ ኃላፊው ገለጻ፣ ምዘናው የ2017 ዓ.ም. አፈጻጸምን መሠረት በማድረግ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን የሚመልስ ብቁና ጠንካራ አመራር ለመፍጠር ያለመ ነው።

በዚህም መሰረት፡-

42 አመራሮች ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል፤

56 አመራሮች እንዲሸጋሸጉ ተደርጓል፤

36 አዳዲስ አመራሮች ወደ ኃላፊነት መጥተዋል።

አቶ ደግፌ አዲስ የተመደቡት አመራሮች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጡ ማሳሰባቸውን የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *