




የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የቦንጋ ማዕከል አስተዳደር ዘርፍ ህብረት ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ኮሚቴ በህብረቱ ውስጥ ለሚገኙ የህብረትና ቤተሰብ አመራሮች በተሻሻለው በብልፅግና ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ፣ በኮሚሽኑ አሰራርና አደረጃጀት መመሪያ ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥተዋል ።
የህብረቱ ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ሰብሳቢ ወ/ሮ ውቢት ደበበ ስልጠናውን አስመልክተው እንደገለጹት በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎችና ውሳኔዎችን ሳይቀራረፍ ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ እገዛ እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ህብረቱ አመራሮች የተቀመጡ ዕቅዶችን ክለሳ በማድረግ በቀጣይ የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ በተናበበ መልኩ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።
በተሻሻለው በብልፅግና ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብና በሌሎች መመሪያዎችና አዳዲስ ድንጋጌዎች ላይ ስልጠና የሰጡት የኮሚሽኑ ህብረት ኮሚቴ አባል ወ/ሮ ውባለም በዛብህ እንደገለጹት የፓርቲው እሴቶች መርሆዎችን መሠረት አድርጎ በመስራት የብልጽግና ህብረት ኮሚሽን አመራሮች ግንባር ቀደም ሚናቸውን እንዲወጡም ገልጸዋል።
በየደረጃው የሚገኝ የፓርቲ ህብረትና የቤተሰብ አመራሮች የተግባርና አስተሳሰብ አንድነት በማጎልበት የውሰጠ ፓርቲ አንድነትን መፍጠር፣ በፓርቲው ውስጥ የፖለቲካ ጤንነት መጠበቁን መከታተልና ማረጋገጥ እንዲሁም
የኮሚሽኑን ተቋማዊ አቅም ሊያጠናክሩ የሚችሉ አሰራሮችና አደረጃጀቶችን ትኩረት ሰጥቶ መስራት አለብን ብለዋል።
የህብረቱ ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚቴ ጸሃፊ የሆኑት አቶ አበበ ገ/ሚካኤል በተደጋጋሚ የሚጣሱ አሰራሮችን ሰነድ ላይ ባደረጉት ገለጻ በየደረጃው የሚገኙ የፓርቲና የኮሚሽኑ አደረጃጀቶችን የአሰራር ስርዓት በማክበርና በማስከበር ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ ሚናችንን መወጣት እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
የህብረቱ ኮሚሽን ሰብሳቢ አንድ ዕቅድ፣ አንድ ሪፖርት አንድ ሚዘና መርህን በመከተልና ለተግባራዊነቱ ሁሉም የህብረትና የቤተሰብ አመራሮች ሚናቸውን መወጣት እንዳለበቸው ገልጸዋል።
