የትምህርት ለትውልድ መርሐ-ግብር የፋይናንስ ክፍተትን በመሙላት እያበረከተው ያለው አስተዋጽኦ፦ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የትምህርት ለትውልድ መርሐ-ግብር በትምህርት ዘርፍ የነበረውን የፋይናንስ ክፍተት በመሙላት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለፁ።



የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሀገር አቀፍ የምክክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመረውን ሰፊ ንቅናቄ ተከትሎ የሚያስፈልገውን ፋይናንስ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ለመሙላት እየተሠራ ነው ብለዋል።
በመረጃ አያያዝ ላይ ያለውን ክፍተት ለማረምም በ2018 የትምህርት ዘመን በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ዲጂታል የመረጃ አያያዝ ተግባራዊ እንደሚደረግ ገልፀዋል።
የትምህርት ቤት ምገባ በትምህርቱ ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት እንዲመጣ እያደረገ በመሆኑ በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎችም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
ለ2018 የትምህርት ዘመን የሚያስፈልጉ የትምህርት ግብዓቶችን ለማሟላት ከወዲሁ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑም ተጠቁሟል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን ![]()
በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
በትዊተር twitter.com/sweprs
በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication
በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
በሊንክደን
