
ዓለም አቀፍ የምግብና የመጠጥ ፎረም በቻይና ሃይናን ግዛት ባኦ ከተማ ዛሬ ተጀምሯል።
በፎረሙ ላይ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ተሳታፊ ሆነዋል።
በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በፎረሙ ኢትዮጵያ ወደ ውጭ የምትልካቸውን የግብርና ምርቶች እያስተዋወቀ እንደሚገኝም ተገልጿል።
በፎረሙ በዓለም አቀፍ የምግብና የመጠጥ ኢንዱስትሪ አሁናዊ ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግ ተመላክቷል።
በዘርፉ የተሰማሩ የኢንዱስትሪዎች፣ ኢንተርፕራይዞች፣ ባለሙያዎችና ምሁራን፣ ዓለም አቀፍ አጋሮችና ሌሎች እንግዶች የፎረሙ ተሳታፊ ናቸው።
ፎረሙ እስከ መስከረም 6/2016 እንደሚቆይ በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
