



በዛሬው ዕለት በመደመር መንግስት እይታ፣ የግብርና እና የኢንዱስትሪ እመርታ በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ በክልሉ በቦንጋ ማዕከል ለሚገኙ የአስተዳደር ክላስተር የብልጽግና ፓርቲ አባላት እየተሰጠ ይገኛል።
የክልሉ የመንግሰት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የመንግስት መረጃና የዲጅታል ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት መስፍን ወዳጆ (ዶ/ር) እንደገለፁት:- ስልጠናው በመደመር መንግስት እይታ የግብርናና የገጠር መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ፣የኢንዱስትሪ ዘርፍ ፣የከተማ ልማት እንዲሁም የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ በሚሉ አጀንዳዎች ላይ እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነቡ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚቀርቡበት መድረክ መሆኑን ተናግረዋል።
በካሳሁን አሰፋ
