የፓርላማና የፌዴሬሽን ም/ቤት የልዑካን ቡድን በዓለም አቀፉ ፓርላማ ህብረት ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ነው

Spread the love

በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር የተመራው የፓርላማና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የልዑካን ቡድን በኡዝቤኪስታን ታሽከንት ከተማ እየተካሄደ ባለው በ150ኛው በዓለም አቀፉ ፓርላማ ህብረት (አይፒዩ) እየተሳተፈ ይገኛል።

በመድረኩ ኢትዮጵያን በመወከል ንግግር ያደረጉት አፈጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር፤ ኢትዮጵያ በህብረቱ ላይ ያላትን አጋርነት አጠናክራ ለመቀጠል ቁርጠኛመሆኗን ገልጸዋል።

ለ2030 የዘላቂ ልማት ግቦች ስኬት የሚመለከታቸው አካለት ዓለም አቀፍ ትብብሮችን እንዲያጠናክሩም ጥሪ አቅርበዋል ሲል ኤፍኤም ሲ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *