




የ2017 የከተማ ልማት ስራዎች የፈጻሚና አስፈጻሚዎች የአፈጻጸም ሂደት በጥንካሬና በጉድለት በሚያሳይ ግምገማዎች እና በቀጣይ የማስፈጸሚያ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ልዩ ረዳት አቶ አለማየሁ አይበራ በመድረኩ እንደገለጹት በብልጽግና ፓርቲ የሚመራ መንግስት ለከተሞች ልማት ከምንጊዜውም በላይ በፖሊሲም ሆነ በተግባር ትኩረት ሰጥቶ እየተገበረ ይገኛል ብለዋል።
ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ በማድረግ የተሰሩት የኮርደር ልማት ስራዎች ከተሞቻችን አረንጓዴ፣ ውብ ንጽህ እና ሳቢ እንዲሆኑ እድል የከፈተ በመሆኑ ልዩ ትኩረት በመስጠት የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደመገባ ጠቅሰዋል።
የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢር ኃላፊ ኢ/ር የማታለም ቸኮል እንደገለጹት ባለፋት ዓመታት በዘርፉ የሚመሩ ሥራዎችን በኃላፊነት ለመፈጸም የተደረጉ አበረታች ጥረቶች ቢኖሩም አሁንም ቢሆን በሙሉ አቅም በኃላፊነትና በተጠያቂነት ስሜት ከመፈጸም እና ከማስፈጸም ረገድ ሰፊ ጉድለት መኖሩን አንስተዋል።
በየጊዜዉ ህዝቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት መንግስት የተለያዩ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ብርቱ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል ።
