የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የአረጋውያን መንደር በመገንባት የትናንት ባለታሪኮችን የመንከባከብ ስራ አጠናክሮ መቀጠሉ ተጠቆመ

Spread the love

‎ዩኒቨርሲቲው ከምርምርና ትምህርት ስራ ጎን ለጎን በተለያዩ ማሕበረሰብ አቀፍ አገልግሎቶች በማከናወን ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑም ተጠቁሟል።

‎በተለይም ጧሪ ደጋፊ የሌላቸውን አረጋውያን ለመደገፍ የአረጋውያን መንደርን በማመቻቸት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡

‎የትናንት ባለታሪክ እና የሀገር ባለውለታ የሆኑ አረጋውያንን ከወደቁበት በማንሳት ዩኒቨርሲቲው ባስገነባው መንደር እየተንከባከበ መሆኑን ገልጸዋል።

‎ተቋሙ በተለያዩ የማሕበረሰብ አቀፍ አገልግሎቶች ላይ እየተሳተፈ አካባቢያዊ ሀብቶችን በማልማት ለሀገር ብልፅግና ሚናውን እየተወጣ ነው ብለዋል፡፡

‎በዋናነት በግብርናው ዘርፍ የምርምር ተግባራትን እያከናወነ ውጤት እንዲመዘገብ ምቹ መደላድልን መፍጠሩን አንስተው÷ በመሰል ተግባራት ላይ የሚከውነውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጧል ሲል ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *