




የክልሉ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊና የክልሉ ሱፐርቪዥን ቡድን አባል የማታለም ቸኮል (ኢ/ር) ፣ ሌሎች የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳድር አመራሮች በቤንች ሸኮ ዞን ሼይ ቤንች ወረዳ ሲዝ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ምልከታ አድርገዋል።
በመስክ ምልከታው በሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቪ እየተሰሩ የእንስሳት እርባታ ማዕከል ሌሎች የልማት ስራዎችን ግብኝተዋል።
የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ የማታለም ቸኮል( ኢ/ር) መንግስት ለግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ የሰጠውን ትኩረትና የዘርፉን አዋጭነት በመረዳት እየተከናወነ ያለው አበረታች ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።
መንግስት ለሰው ተኮር ለሆኑ የልማት ዘርፎች የሰጠውን ትኩረትና በአጭር ጊዜ ከድህነት ለመላቀቅ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላክት እንደሆነም ተገልጿል።
