የተገለጠ ዓይን ሲኖር የኢትዮጵያ የብልፅግና ጉዞ የተቃና ይሆናል:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Spread the love

ዛሬ የጎበኘነው ልማት የሚያሳየው የተገለጠ ዓይን እና የጠራ ሃሳብ ሲኖር በአጠረ ጊዜ ውስጥ ሀገር መቀየር የሚያስችል ዕድል መኖሩን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዳውሮ ዞን የተገነባውን የኢቲ ማዕድን ልማት አ.ማ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት፥ እንዲህ ያለው ዕድል ተግቶ የማየት እና የመስራት ልምምድ ሲጨመርበት ደግሞ በአጭር ጊዜ ከድህነት ለመውጣ እንድንችል ያደርገናል ብለዋል።

ከለውጡ በኋላ ኢኮኖሚው ብዝኃ ዘርፍ እንዲሆን በማድረግ አዲስ የእይታ መስክ ተፈጥሮ ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል።

ይህን ተከትሎ ከዚህ በፊት በቱሪዝም እና በማዕድን ልማት እምብዛም የማይታወቀው ዳውሮ ዞን ቀደም ሲል በሀላላ ኬላ የቱሪስት መዳረሻ የጀመረው የአካባቢው ለውጥ አሁን ደግሞ በማዕድን ልማት ቀጥሎ የአካባቢው እምቅ አቅም እየወጣ መሆኑን ጠቁመዋል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *