ርዕሰ መስተዳድሩ ለምክርቤቱ አባላት ባቀረቡት የ6 ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት በማህበራዊ ልማት ዘርፍ ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የሚከተሉትን ነጥቦች አንስተዋል ፡፡ከእነዚህም መካከል

Spread the love

👉 የትምህርት ለትውልድ ኢንሼትቭ ስራዎችን ውጤታማ ለማደረግ በጥሬ ገንዘብ፣ በአይነት እና በጉልበት 142,146,033 ብር ተሰብስቧል፡፡

👉 የቱልጊት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉና በክልሉ መንግስት ድጋፍ እየተገነባ ሲሆን ግንባታዉ ከ 90% በላይ ማድረስ ተችሏል፡፡

👉የትምህርት ተሳትፎ ከቅድመ አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል 734,496 ተማሪዎች በመማር ላይ መሆናቸው፡፡

👉 የአንደኛ ደረጃ መማሪያ መጽሐፍ በህብረተሰብ ተሳትፎ ብር 161,205,719 እና ከመንግስት 60,000,000 ብር በድምሩ 221,205,719 ብር ተሰብስቦ 1,023,837 መጽሐፍ በማሳተም ተሰራጭቷል፡፡

👉 የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የስታንዳርድ ኦዲት በማከናወን ከስታንደርድ በታች የሆኑ 11 የግል ኮሌጆች የተዘጉ ሲሆኑ 9 ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

👉 ቴክኒክና ሙያ ስልጠና የገቡ ሰልጣኞች በመደበኛ ነባር ሰልጣኞች 5856 ፣ አዲስ ሰልጣኞች 4480 ተከናዉኗል፡፡

👉 የውጪ አገር ስራ ስምሪትና ስልጠና ለ 3179 ዜጎች ተከናዉኗል፡፡

👉 የስራ ዕድል ፈጠራ በቋሚ 18,200 በጊዜያዊ 81,738 በድምሩ 99,938 መፍጠር ተችሏል።

👉 ውጭ ሀገር ሄደው ለመስራት የሚፈልጉ 209 ዜጎች ከኢምግሬሽንና የዉጭ አገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ የስራ ዕድል እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡

👉 የወባ በሽታ መከ/መቆጣጠርን በተመለከተ ምርመራ ከተደረገላቸው 1,179,849 ሰዎች ውስጥ 750,489 ሰዎች የወባ ተዋሲያን በደማቸው የተገኘባቸው ሲሆን የወባ የመገኘት ምጣኔ 63.6% ደርሷል፡፡

👉 ኤች አይ ቪን ለመከላከልና ለመቆጣጠር 90,348 ምርመራ የተከናወነ ሲሆን 580 ሰዎች ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ተገኝቷል፡፡

👉 በሰለጠኑ የጤና ባለሙያዎች 30,721 እናቶች የወሊድ አገልግሎት አግኝተዋል፡፡

👉 የደም ባንክ አገልግሎት 1193 ዩኒት ደም ተሰብስቧል፡፡

👉 የጤና ተቋም መሰረተ ልማት ግንባታዎችን የማስጨረስና ለረዢም ጊዜ ግንባታቸዉ የቆሙትን ዉለታ በማቋረጥ በክልሉ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ዉል በመግባት እየተገነቡ ይገኛሉ፡፡

👉 የሴቶችን የሥራ ጫና ለማቃለል 29,960 ሴቶች ዘመናዊ የሆኑ ጊዜ እና ጉልበት ቆጣቢ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቃሚ ሆነዋል ፡፡

👉 644,558 በክረምት የወጣቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተሳትፈዋል።

👉 2,619,560 የህብረተሰብ ክፍሎች በወጣቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል፡

👉 የተከናወኑ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባራት በገንዘብ ሲተመን 604,422,460 መፈጸም ተችሏል፡፡

👉 በ 11 የቅርስ የስብስብ ማዕከላት 1472 ቅርሶች ተሰብስበዋል፡፡

👉 በቱሪዝም ዘርፍ የሥራ ዕድል በቋሚ 427 በጊዜያዊ 2501 ተከናዉኗል፡፡

👉 ልዩ ልዩ ሀገር በቀል ዕውቀቶች እንዲጠኑ፣ እንዲጠበቁና እንዲለሙ ተደርጓል

👉 የህዝብ ለህዝብ ትስስር በሚያጠናክሩ ኩነቶች የዘመን መለወጫ ክብረ- በዓላት በጋራ ተከብሯል፡፡

👉 በክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ዉድድር በማካሄድ 8,914 ስፖርተኞችንና አትሌቶችን ማሳተፍ መቻሉን ርዕሰ መስተዳድሩ በሪፖርታቸው አቅርበዋል።

በታጠቅ አበበ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *