
ኢትዮጵያ የተሻለ ቁመና ያላቸውን ተቋማት ፈጥራለች፣
ባለፈው ዓመት የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሀገር ደረጃ 18 ደርሷል፤ በቅርቡ 3 የሚጨመር ሲሆን በዚህ ዓመት 100 ለመድረስ እንሰራለን፣
መሬት፣ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ ንግድ ፍቃድ፣ ግብር ላይ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ ነው፣
የዛሬ 3 ዓመት ኢትዮጵያ ለፓስፖርት ፈላጊ ዜጎች ማቅረብ የምትችለው 270 ሺህ ነበር፤ በዚህ ዓመት 4 ሚሊየን ነው የምታቀርበው፣
በኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እየተካሄዱ ያሉ ሪፎርሞች ውጤት እያመጡ ነው፣
ዲጂታል በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያመጣው ለውጥ ከፍተኛ እንደሚሆን ይጠበቃል፤ 55 ሚሊየን ሰዎች ሞባይል ባንኪንግ ይጠቀማሉ፣
ጂኤስኤም ባወጣው ሪፖርት በ2028 የዲጂታል ቴክኖሎጂው 11 ቢሊየን ዶላር ገደማ ሀብት ያመጣል፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ለ1 ሚሊየን ሰዎች የስራ ዕድል ይፈጥራል።
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን ![]()
