በክልሉ መረጃዎችን የመሰብሰብ ስራ ወረቅት አልባ በሆነ ቴክኖሎጂ ተጠናክሮ እንደሚሰራ ተገለጸ

Spread the love

ሀገር አቀፍ የመንግስት ሰራተኞች ፐርሶናል መረጃ ሀገር አቀፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ መድረኩ በልዩ ሁኔታ የሚፈጸም ተግባር ተልዕኮን ለማከናወን ወሳኝ መሆኑን አመላክተዋል።

ባለፉት 8 የለውጥ ዓመታት ከመጡ መሠረታዊ ለውጦች አንዱ የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን ያስረዱት አቶ ሳምሶን ስራዎችን ወረቀት አልባ በሆነ አሰራር መፈጸም አንዱ ኃላፊነት መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚህ ስልጠና በኋላ በክልሉ ሁሉም ተቋማት የመንግስት ሰራተኞች ቆጠራ በተደራጀ መንገድ እንደሚከናወንም ገልጸዋል።

ተቋማት ተገቢውን መረጃ በመሰብሰብ ፣በማደራጀት ለሚመለከተው አካል በተገቢው ተደራሽ ማድረግ ግዴታቸውም መሆኑንም አቶ ሳምሶን አሳስበዋል።

በመድረኩ የተገኙት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሚዛን አማን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሽመልስ መጀቶ የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ማረጋገጫ ስራ ከመደበኛ የአስተዳደር ስራ ባለፈ ለሀገራዊ ሪፎርም መሠረታዊ ምሰሶ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የፐርሴኖል መረጃ ማረጋገጥ ስራ ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ፣ አገልግሎትን ለማዘመን፣ ለሀብት አጠቃቀምና ትክክለኛ ፖሊሲዎችን ለመንደፍ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አቶ ሽመልስ ተናግረዋል።

በመድረኩ ሀገር አቀፍ የመንግስት ሰራተኞች ፐርሶኔል መረጃ ማረጋገጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ ወርክሾፕ የውይይት ሰነድ በአቶ ዓለሙ ደኣ ከፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንና በወ/ሮ ሶርሴ ጉተማ ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጥናትና ምርምር እና ስልጠና መሪ ስራ አስፈጻሚ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር በተዘጋጀው የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች የመረጃ ማረጋገጫ ስራ ከክልል ተቋማት እና ከዞንና ወረዳ የተውጣጡ የሰው ሀብት ዳይሬክተሮች ተሳታፊ ናቸው ሲል ቤሸቴ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *