የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የዉክልና ሥራ የማጠቃለያ መድረክ በቦንጋ እየተካሄደ ነው




የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በክልሉ ከወከላቸው ህዝቦች ጋር ያደረጉትን ውይይትና የመስክ ምልከታን በማስመልከት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች ጋር የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ የተከበሩበአቶ ወንድሙ ኩርታ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት የህዝብ ተወካይ ምክር ቤት አባላት ከመረጧቸዉ ህዝቦች ጋር ዉይይት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
ዛሬ በሚቀርበዉ ግብረ መልስ ከአስፈጻሚ አካላት ጋር ዉይይት የሚደረግ ሲሆን በክልሉ በፌደራል መንግስት የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ላይ ከምክር ቤት አባላቱ ጋር ምክክር እንደሚደረግ ጠቅሰዋል።
በዚህም በመስክ ምልከታ ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን በቀረበው የመስክ ሪፖርት መነሻ በማድረግ በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት የሚደረግም ይሆናል።
በመድረኩም የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸዉን ጨምሮ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ፣የክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎችና የክልሉ መንግስት አስፈፃሚ አካላት እየተሳተፉ ነው።
በተከተል ወ/ሚካኤል
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን ![]()
በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
በትዊተር twitter.com/sweprs
በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication
በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
https://www.linkedin4v .com/company/southwest-communications/
