በዘንድሮው የበልግ አዝመራ 12 ሚልዮን የእንሰት ችግኝ ለመትከል እየተሰራ መሆኑን በሸካ ዞን የአንድራቻ ወረዳ ግብርና ደን አከባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ፅ/ቤት አስታወቀ ።

Spread the love

አሁን ላይ ከእንሰት ተክል አስተዋፅኦዎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ ምክንያት በዘርፉ ጥናትና ምርምሮች እየተከናወኑ መሆናቸውን መረጃዎች ያመላክታሉ።

በዚህም እንሰት ለምግብነትና ለተለያዩ የቤት ቁሳቁስ ሆኖ ከመዋል አልፎ ተረፈ ምርቱ በፋብሪካ ውስጥ ገቢቶ ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ በመሆኑ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ተስጥቶ እየተሰራ ይገኛል።

የአንድራቻ ወረዳ እርሻ፣ደን፣አከባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ፅ/ቤት በበጀት ዓመቱ 12 ሚሚልዮን የእንሰት ችግኝ ለመትከል ቅድመ ዝግጂት እያደረገ እንደሚገኝ የገለጹት የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አክሊሉ ሸነኖ ከባለፈው አመት ጀምሮ የችግኝ ዝግጅት እንዲደረግ ከአርሶ አደሮች ጋር በመግባባት ሰፋፍ ስራዎች ስሰሩ መቆየቱን አመላክተዋል።

በተያዘው አመት የተጣለውን ግብ ለማሳካት በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ልደግፉና በጋራ መስራት እንደሚገባም ጽ/ቤቱ አሳስበዋል ሲል ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *