

የውጭ ግንኙነት ማዕከል እና መሰረታዊ ማጠንጠኛው ብሔራዊ ጥቅም እና የዜጎች ክብር ነው አሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ።
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት እና የፌዴሬሽን ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
ምክር ቤቶቹ ዓመታዊ ሥራቸውን እንደጀመሩ ያበሰሩት ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፤ የኢትዮጵያ ጂኦስትራቴያጂያዊ ቁመና በመደርጀት ላይ ይገኛል ብለዋል።
ይህም ከታዛቢነት ወደ አጀንዳ ተላሚነት እና ተጽዕኖ ፈጣሪነት ለማሸጋገር አስችሏል ብለዋል።
