




የናይጄሪያ ወታደራዊ ሪሶርስ ማዕከል ልዑካን ቡድን አባላት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መሥሪያ ቤት የለውጥ ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝታቸውም፤ ዘመናዊ የፖሊስ መገናኛ ዲጂታል ሬድዮ፣ የኮማንድ ኮንትሮል ማዕከልን፣ የቀጥታ ጥቆማ መቀበያ፣ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያና ዘመናዊ ካሜራና የደኅንነት መሣሪያ የተገጠመላቸው ልዩ ልዩ ተሽከርካሪዎችን ተመልክተዋል፡፡
የተቋሙን ተልዕኮ፣ አደረጃጀት፣ እሴቶችና ዓላማ በተመለከተ የፌደራል ፖሊስ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ትብብር ዋና መምሪያ ተጠባባቂ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ደጀኔ በቀለ ገለጻ አድርገዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላትም በጉብኝታቸው ባዩት ነገር መደሰታችውን ገልጸው፤ ለተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ምሥጋና ማቅረባቸውን የፌደራል ፖሊስ መረጃ ያመለክታል ሲል ኤፍኤም ሲ ዘግቧል፡፡
