ርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ-ልማት ዘርፍ አፈጻጸምን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

Spread the love

👉በስድስት ወራት ዉስጥ ብዙ ንጹህ መጠጥ ዉሃና የመስኖ ልማት ተቋማትን በማስመረቅ ለአገልግሎት ብቁ ማድረግ ተችሏል።

👉263.854 ኪ.ግራም ኪ/ግ ወርቅ ለብሄራዊ ባንክ ገቢ ማድረግ መቻሉ፣

👉ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚውሉ 90ሺህ 180 ቶን የድንጋይ ከሰል ማምረት ተችሏል፡፡

👉ከሮያሊቲ ገቢ እና ከማዕድን ስራዎች 107ሚሊዮን 912ሺህ 300.86 ብር መሰብሰብ ተችሏል፡፡

👉በከተሞች መሠረተ-ልማት ግንባታ ነዋሪዉ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ተጠቃሚነቱን እንዲያረጋግጥ ከህብ/ሰቡ ከ81ሚሊዮን 331ሺህ ብር የሚገመት የገንዘብ፣ የጉልበትና ዓይነት በማሰባሰብ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል፡፡

👉በከተሞች የመኖሪያ ቤት እጥረት ለመቅረፍ 3ሺህ164 መኖሪያ ቤቶች ፤ በገጠር የልማት ማዕከላት ደረጃቸዉ የተሻሻሉ 1ሺህ166 ቤቶችን መገንባት ተችሏል፡፡ 170 የመንግስት ቤቶች መረጃ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲደራጅ ታቅዶ 298 ቤቶች መረጃ በቴክኖሎጂ እንዲደራጅ ተደርጓል፡፡

👉በክልሉ እየተገነቡ ያሉ 3 መናኃሪያዎች አፈጻጸማቸው የቦንጋ 85% ፣ የታርጫ 96%፣ እንዲሁም የሚዛን 96% ማድረስ ተችሏል፡፡ ቀሪ ስራዎችን በማጠናቀቅ በቅርብ ጊዜ የሚመረቁ ይሆናል፡፡

👉17ሺህ 954 ተሽከርካሪዎች ላይ የትራፊክ ቁጥትር በማድረግ 942 አሽከርካሪዎች ከታሪፍ በላይ በማስከፈላቸው እርምጃ ተወስዶ በዚህም ለ12ሺህ 943 ተሳፋሪዎች 1ሚሊዮን 533,506 ብር ማስመለስ ተችሏል፡፡

👉በመንገድ ለመሠረተ ልማት ግንባታ የህብረተሰብ ተሳትፎና ባለድርሻ አካላት በማሳተፍ 221ሚሊዮን 599ሺህ 384 ብር ማሰባሰብ ተችሏል፡፡

👉የአርብቶና ከፊል አርብቶ አደር ልጆችን በሆስቴሎች በድምሩ 179 ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ታቅዶ 172 ተማሪዎች ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ፡፡

👉በአርብቶ አደር አካባቢ የሚታየውን የተማረ የሰው ኃይል እጥረት ለመቅረፍ በሁለተኛ ዲግሪ 02፣ በመጀመሪያ ዲግሪ 90 እና በዲፕሎማ 18 ተማሪዎች ትምህርታቸውን በተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡

👉በውሃ እና የመስኖ አውታር የጥናትና ዲዛይን እንዲሁም የግንባታ ሥራዎች በክልሉ መንግሥት የበጀት ድጋፍ መከናወናቸውን ርዕሰ መስተዳደሩ በሪፖርታቸዉ ጠቅሰዋል።

በዕድገቱ በዛብህ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *