

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2032 በአፍሪካ ሁለተኛው ቀዳሚ ኢኮኖሚ በ2036 ደግሞ ከአፍሪካ ቀዳሚው ኢኮኖሚ እንደሚሆን ተናግረዋል።
ይህን ለማሳካት ግን ሁሉም በጋራ መሥራት አለበት ሲሉ ገልፀዋል።
አሁን እየሄድንበት ያለው መንገድ ይህን ያመላከተ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አይኤም ኤፍ የኢትዮጵያን እድገት አድንቀዋል ብለዋል።
