




በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ”ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ማኒፌስቶ እና ምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
የፓርቲዉ ማኒፌስቶ እና የምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መርሐ -ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
የብልጽግና ፓርቲ የ7ኛው ሀገራዊ የምርጫ ምልክት ”የሰንዴ ነዶ” ሲሆን ምልክቱ የመደመር ፣ አንድነት እና ትብብር መገለጫዎችን የያዘ ነዉ።
በመርሃ ግብሩ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ጨምሮ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስትና ፓርቲ አመራሮች፣ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በፍቅር ከበደ
