




በሚዛን -አማን ከተማ በአማን አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች የምግባ ፕሮግራም በይፋ ተጀምሯል።
የትምህርት ቤት የምገባ መረሐ -ግብር መተግበር ለትምህርት ተሳትፎና ውጤታማነት የችግሮቹ ቁልፍ የመፍቻ መንገድ ሆኖ በመገኘቱ እንደ ሀገር እየተሰራበት ይገኛል።
በቤንች-ሸኮ ዞን ባሉ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ትምህርት ቤቶች የምገባ ፕሮግራም ከባለፈው አመት ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉን የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ አገኘሁ ወርቁ ገልፀዋል።
በዞኑ ወደ 277 ትምህርትቤቶች ሲኖሩ ከዚህ ውስጥ ቅድመ አንደኛ ጀረጃ ትምህርት የሚያስተምሩ 211 ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን አመልክተው በ2017 የትምህርት ዘመን በ126 ትምህርት ቤቶች ላይ የተማሪዎች ምገባ መደረጉን ገልፀዋል።
በዘንድሮው አመት በዞኑ ባሉ ወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች በሁሉም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የምገባው መርሐ ለማካሄድ እቅድ ተይዞ ወደ ስራ እንደተገባ ተናግረዋል ።
በዚህ መሠረት የዘንድሮው አመት የተማሪዎች ምግባ መርሐ-ግብር በሁሉም ትምህርትቤቶች በይፋ ስለመጀመሩ የአማን ትምህርት አንዱ ማሣያ ነው ብለዋል።
ለምገባው መርሐ -ግብር እውን መሆን የተማሪ ወላጆች ባላሀብቶች የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሣተፋ እየተደረገ ነው ያሉት ሀላፊው ትምህርትቤቶችም ከውስጥ ገቢያቸው 20 በመቶ ለዚህ አለማ እንዲያውሉ እንደተደረገም አመልክተዋል።
በትምህርት ቤቶች ምግባ መካሄዱ ተማሪዎች ትምህርታቸው ሳያቋርጡ በንቃት እንዲከታቱ ከማድረጉ ባለፈ በስነ-ልቦናም በአካልም ጠንካራ እንዲሆኑ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል ።
የሚዛን-አማን ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደረጀ ኪዊክ በበኩላቸው ባለፈው አመት በሁለተኛው መንፈቅ አመት የተማሪዎች ምገባ መርሐ-ግብሩ መካሄዱን አስታውሰው ምገባውም በ23 ትምህርት ቤቶች መደረጉት ገልፀዋል።
በዘንድሮው አመት በ23 ትምህርትቤቶች የምገባው መርሐ-ግብር እንደሚካሄድ እና ዛሬ በአማን ትምህርት ቤት መጀመሩን አመልክተዋል።
ምገባው በተማሪዎች መሀከል ይፈጠር የነበረው የአመጋገብ ልዩነት የፈታና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ትምህርት ቤት እንዲመጡ ና እንዲቆዩ በማድርግ የትምህርት ተሳትፎ እንዲያድግ አስተዋፅኦ አድርጓል ብለዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የአማን ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ፎታ የተማሪዎች ምገባ መጀመሩ ለትምህርት ስራው አጋዥ ስለሆነ ለምገባው ስራ በቀበሌው የሚገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማወያየት እየተሰራ ያለው ስራ ውጤታማ እንደሆነ ተናግረዋል።
የአማን የመጀመሪያና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ር/መ ከድር ሀምዛ በበኩላቸው ባለፈው አመት በትምህርት ቤቱ ምገባ ከ215 በላይ ተማሪዎች መገልገላቸውን አመልክተው መርሐ-ግብሩ መካሄዱ ተማሪዎች በሰአት እንዲመጡ ከማድርግ ባፋለ በተማሪዎች ስነልቦና ላይ ይደረስ የነበረውን ጫና እንዲቀንስ አድርጓል ብለዋል።
በምገባ ማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የዞኑ ትምህርት መምሪያ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የመማሪያ ቁሣቁስ ድጋፍ መደረጉን ቤንች ሸኮ ቴቪ ዘግቧል።
