በዚሁ ክልላዊ የወጣቶች ክንፍ የውይይት መድረክ ከ700 በላይ ወጣቶች እንደሚሳተፉ ከወጣው የድርጊት መርሃ ግብር ማወቅ ተችሏል።
የወጣቶች ክንፍ የውይይት መድረክ በተዋረድ እስከ ቀበሌ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ታውቋል።
ከውይይቱ ባሻገርም ወጣቶች የደም ልገሳ ፕሮግራም እንደሚያደርጉም ታውቋል።
ከክልሉ ሁሉም ዞኖች የተውጣጡ የወጣቶች ክንፍ ትናንት በከተማው እየተከናወኑ ባሉ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።