በብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ስራ አስፈፃሚ አባላትበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት “በሴቶች ተሳትፎ የፀናችና የበለፀገች ኢትዮጵያ!” በሚል መሪ ቃል በነገው ዕለት ለሚካሄደው መድረክ ቦንጋ ከተማ ገቡ

Spread the love

በብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ አስተባባሪዎች ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ስራ አስፈጻሚና ደቡብ ኢትዮጲያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ፣ዶ/ር ፈለቀች ተክለማርያም ሴቶች ክንፍ ስራ አስፈጻሚና የማእከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ፕላን ቢሮ ምክትልሀላፊ ፣ኢንጅነር ትዕግስት ተረፈ የሴቶች ክንፍ ስራ አስፈጻሚና የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ም/ፕሬዝደንት ጊምቦ ወረዳ ኡፋ ከተማ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

በአቀባበሉም ስነስርዓት የደቡብ ምዕራብ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰበለጸጋ አየለ ፣የጽ/ቤቱ ም/ ኃላፊ ወይዘሮ ዉባለም በዛብህ ፣ የካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወይዘሮ እታገኝ ወልዴ ፣ የክልል፣ የዞንና የጊምቦ ወረዳ ሴት አመራሮች እና አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።

የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አስፈፃሚዎች በጊምቦ ወረዳ በኡፋ ከተማ በሴቶች ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ላይ በክንፉ አባላት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ምልከታ አድርጓል ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *