በዳታ ቤዝ መረጃዎችን ወጥነት ባለው መልኩ ተደራሽ በማድረግ ረገድ ክልሉ እየሰራ መሆኑ ተጠቆመ።

Spread the love

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የፕላንና ልማት ቢሮ ምክትልና የልማት መረጃና ስነ ህዝብ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሰለሞን አየለ እንደገለፁት መረጃዎች ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ በመሰብሰብና በማጥናት ለማህበራዊና ኢኮኖሚያ ልማትና ዕድገት ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል።

የተቀናጀ የመረጃ ስርዓትን በመዘርጋት መረጃን ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

መረጃዎችን በቴክኖሎጂ አማካኝነት ለመረጃ ፈላጊ ለሀገራዊ የልማት ሥራዎች ማቅረብ ይገባል ብለዋል።

መረጃዎችን በማጠናከር በመረጃ ቋት እንዲገቡ በማድረግ ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ በክልሉ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት እና በልማት ድርጅቶች የክልሉ ዳታ ቤዝ እንዲደራጅ መደረጉን አቶ ሰለሞን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሚዛን ቅ/ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሽመልስ መጪቶ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባለፉት 60 ዓመታት መረጃዎችን አደራጅቶ በማቅረብ በርካታ ሥራዎችን እንደሰራ ተናግረዋል።

በአንድ ቋት የሚተዳደር መረጃ ያለው የሀገር የኑሮ ደረጃን የሚያመላክት፣የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ያለው ተቋም መሆኑን ተናግረዋል።

በሀገሪቱ ካሉ 26 ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ውስጥ አንዱ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚዛን መሆኑን አቶ ሽመልስ ጠቁመዋል።

ክልሉ ከተደራጀ ወዲህ መረጃዎችን በራሱ የመረጃ ቋት እንዲይዝ በርካታ ሥራዎች መሰራታቸውንም አክለው ተናግረዋል።

አቶ ሽመልስ አክለውም የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በክልሉም እየተካሄደ መሆኑንም ገልፀዋል።

በመድረኩ የለማው ዳታ ቤዝ የማስተዋወቅና ተያያዥ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ፣UNFPA እና የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ በጋራ የተዘጋጀ መድረክ ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *