ኢትዮጵያና አልጄሪያ በወጣቶች የድንበር ተሻጋሪ በጎፈቃድ አገልግሎት በጋራ ለመስራት ተስማሙ

Spread the love

የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና ከአልጄሪያ አቻቸው ሙስተፍ ሂደዊ ጋር ተወያይተዋል።

ፕሬዝዳንቶቹ ከአራተኛው የፓን አፍሪካ የወጣቶች ጉባኤ ጎን ለጎን ነው የሁለትዮሽ ውይይት ያካሄዱት።

በውይይታቸውም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በወጣት ፕሮግራሞች ልውውጥ በጋራ ለመስራት መምከራቸው ተገልጿል።

ፕሬዝዳንቶቹ የወጣቶች የድንበር ተሻጋሪ በጎፈቃድ አገልግሎትን ለማስጀመር ከስምምነት መድረሳቸውም ተመላክቷል።

ከስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች ወደ ስራ ለማስገባትና የመግባቢያ ስምምነት ለመፈራረም የሚያስችል የቴክኒክ ቡድን መቋቋሙን የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት መረጃ ያመለክታል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *