





እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚታየውን አመግባባት ለመፍታት አካታች እና አሳታፊ በሆነ መልኩ ምክክር ማድረግ ወሳኝ ጉዳይ ነው።
ኢትዮጵያም ይህንኑ አምናበት ሁሉም ዜጎች የሚሳተፉበት ምክክር በማድረግ ላይ ትገኛለች።
እርስዎም ሀሳብዎ ለሀገራችን ችግሮች መፍትሄ እንደሚሆን አውቀው በምክክሩ በንቃት ይሳተፉ!
ኮሚሽኑ በመጪው እሁድ ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚጀምረው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ የቅስቀሳና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ በማከናወን ላይ ነው።
