የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

Spread the love

የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ከነሷቸው ጥያቄዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል

. በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ታጥቀው ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት ምን እየተሠራ ነው?

. የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? ፤ በትግራይ ዳግም ጦርነት እንዳይነሳስ ምን እየተሠራ ነው?

. የፍትሕ ተደራሽነት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመሰረቱ ለመፍታት መንግሥት በቀጣይ ምን ለመስራት አስቧል?

. በሰላም እጦት ሳቢያ በበርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሕዝብ ላይ የሚደርሰውን እንግልትን ከመሰረቱ ለመፍታት ምን እየተሠራ ነው?

. በአምራች ዘርፉ ያለውን የጥሬ ዕቃ እና የሌሎች የአቅርቦት ችግሮ ለመፍታት መንግሥት ምን እየሠራ ይገኛል?

. የ10 ዓመቱን ስትራቴጂክ ዕቅድ ማሳካት መቻላችን አመላካቾቹ ምን ምን ናቸው? ፤ ሴክተሮችስ ከዚህ ዕቅድ ጋር ተናብበው እየሠሩ ናቸው?

. መንግሥት በድጎማ የሚያቀርበው ነዳጅ በሕገወጥ መንገድ እንዳይሸጥ ለማድረግ ምን እየሠራ ይገኛል?

. በአሁኑ ሰዓት የመንግሥት ሠራተኛን ጨምሮ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በኑሮ ውድነት እየተቸገሩ ባሉበት ሁኔታ እንዴት የዋጋ ግሽበት ቀንሷል ይባላል?

. የቁጥጥር ተቋማት ነጻ ሆነው በትክክል ኃላፊታቸውን እንዲወጡ ለምን አይደረግም?

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *