ኢትዮጵያ በዱባይ እየተካሄደ ባለው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነው

Spread the love

ኢትዮጵያ “ደህንነቱ ለተጠበቀ ነገ ዓለም አቀፍ የፖሊስ ኃይል ትብብር” በሚል መሪ ሀሳብ በዱባይ እየተካሄደ ባለው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነው።

በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የተመራው ልዑክ በፈረንጆቹ ከመጋቢት 5 እስከ 7 ቀን 2024 በዱባይ እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ልዑካን ቡድኑ በቦታው ሲደርስ በዱባይና ሰሜን ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ቆንሰላ ጀነራል ፅ/ቤትና በአቡዳቢ የኢፌዲሪ ኤምባሲ አቀባበል ተደርጎለታል።

ኮሚሽነር ጀነራሉ ከዱባይ ፖሊስ ዋና አዛዥ ሌተና ጀነራል አብዱላህ ከሊፋ አል ማሪ ጋር መሥራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የጎንዮሽ ውይይት አድርገዋል ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *