በዳውሮ ዞን 59 አመራሮች ከኃላፊነታቸው ተነሱ

Spread the love

በዳውሮ ዞን በቅርቡ በተደረገ ጥብቅ ግምገማ ላይ ተመስርቶ በተወሰደው እርምጃ ከዞን አስከታችኛዉ መዋቅር 59 አመራሮች ሙሉ በሙሉ ከኃላፊነታቸው የተነሱ ሲሆን፣ ሌሎች 55 አመራሮች ደግሞ የኃላፊነት ሽግሽግ ተደርጓል።

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ኢዮብ ቶማስ እንደገለጹት፣ ይህ እርምጃ የተወሰደው ያለፈውን ዓመት አፈጻጸም ከመዘነ በኋላ መጪውን ተልዕኮ በብቃትና በስነ ምግባር ሊያስፈጽም የሚችል ጠንካራ አመራር ለመፍጠር ነው።

በዚህም መሰረት 35 አዳዲስ አመራሮች ወደ ኃላፊነት የመጡ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 149 አመራሮችን ያካተተ ከኃላፊነት የማንሳት፣ የማሸጋሸግና አዲስ ምደባ ተከናውኗል ማለታቸዉን የዞኑ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *