




የክልሉ ጤና ቢሮ እናቶች፤ ህፃናት አፍላ ወጣቶች ጤና እና ስነ-ምግብ ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ.ም እና የ2018 ሩብ ዓመት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ጤና ቢሮ ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሀይሌ ዘውዴ ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ የጤና ተቋማትን ለማስፋፋት በሰጠው ትኩረት አዳዲስ ጤና ተቋማት ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በክልሉ 138 ጤና ተቋማትና 817 ጤናኬላዎች ከ የጤና አገልግሎት እየሰጡ ቢሆንም ከአገልግሎት ጥራት አንፃር የሚታዩ ውስንነቶች ሊቀረፉ እንደሚገባ ተናግረዋል።
አቶ ኃይለ አክለውም ምቹ የእናቶች ማቆያ በማዘጋጀትና ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት በመስጠት የእናቶችና ህፃናት ሞት መቅረፍ እንሚመገባ ገልዋወል።
በእናቶች ምርመራና ወሊድ አገልግሎት አሰጣጥ ረገድ
በ2017 የተደራጀ ስራ መከናወኑን የጠቆሙት አቶ ኃይለ የወጣቶችና አፍላ ወጣቶች የቤተሰብ ዕቅድ ዙሪያ የታዩ ክፍተቶች መሻሻል እንዳለባቸው ገልጸዋል።
የህፃናት ክትባት፤ የእናቶች ማቆያ ግንባታ፤ የአፍላ ወጣቶች ቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትና የድህረ ወሊድ አገልግሎት ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባም ኃላፊው ተናግረዋል።
በዳይሬክቶሬቱ የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማጠናር ውስንነቶችን ለማሻሻል ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባም ኃላፊው ገልጸዋል።
የክልል ጤና ቢሮ እናቶች፤ ህፃናት አፍላ ወጣቶች ጤና እና ስነ-ምግብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሠረት ወ/ማሪያም በበኩላቸው በክልሉ ምስረታ ወዲህ በዘርፉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ውይይቱ በተግባራት አፈፃፀም ወቅት የሚታዩ ክፍተቶች ለማሻሻል ግብዓት የሚሰበሰብበትና ክፍተቶችን ለማሻሻል የሚረዳ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
በመድረኩ የዞኖችና በየደረጃው ያሉ ጤና ተቋማት የ2017 ዓ.ምና የ2018 ሩብ ዓመት አፈፃፀም ቀርቦ የሚገመገም ይሆናል።
በውይይቱ የክልሉ ጤና ቢሮ የስራ ኃላፊዎች፤ የዞን፤ የወረዳ እና በየደረጃው ያሉ ተቋም ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ ሲል ደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።
