BLOGS

በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎች በማስፋት ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ትኩረት ሰጥተው መስራት ይጠበቅባቸዋል፦ አፈጉባኤ ክቡር አቶ ወንድሙ ኩርታ

በክልሉ ምክር ቤት አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው 7ኛ ዙር ፎረም ላይ የተሳተፉ የክልልና የዞን አመራሮች ልዑክ በሚዛን አማን ከተማ አማን ቀበሌ የመስክ ጉብኝት አካሂዷል። በመስክ ምልከታው ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈጉባዔ አቶ ወንድሙ ኩርታ የክልሉ ብሔረሰብ ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶጌታቸው ኬኒን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞን ምክር አባላቶች ተሳታፊዎች ሆነዋል። አፈጉባኤዎቹ ጉብኝታቸው በአማን ቀበሌ እየተከናወኑ ያሉ…

Read More

ኅብረ-ብሄራዊ አንድነትን የሚፈታተኑ የፊውዳል አስተሳሰቦችን በጽናት መታገል ይገባል” – ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን፤ በሞዲዮ የፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም ያሰለጠናቸውን የ1ኛ ዙር መደበኛ ፖሊስ አባላትን ዛሬ በደመቀ ሁኔታ አስመርቋል። በምረቃው መርሃ-ግብር ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ለተመራቂዎቹ የሥራ መመሪያ የሰጡት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፤ ተመራቂ ፖሊሶች ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በመጠበቅ የፍትሕ መከበርን እንዲያረጋግጡ አሳስበዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ተመራቂዎች የተጣለባቸውን ሕዝባዊ…

Read More

በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ ከ49 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው የፋንታ አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክት የመሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ።

በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ ባዛ ሾታ ቀበሌ በፓክት (PACT) – በተሳትፎአዊ ግብርናና አየር ንብረት ሽግግር ፕሮግራም አማካኝነት የሚገነባው የፋንታ አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክት ግንባታ በይፋ ተጀምሯል። የፕሮጀክቱን መሠረተ ድንጋይ ያስቀመጡት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ምክትል ርዕሰ መሰተዳድና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸዉ የፋንታ አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክት በክልላች የግብርናውን ዘርፍ እየተካሄደ ያለውን የብልጽግና ጉዞ…

Read More

ማዕከሉ ፈጣንና ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በመስጠት ከዚህ ቀደም ይስተዋል የነበረ የህዝብ ቅሬታ መፍታት እያስቻለ ነው፦ የክልሉ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት

‎አገልግሎቱን ለማስፋት ታልሞ በተከናወነ ስራ በዞኖች አካባቢ የተጀመሩ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተቋማት ግንባታ ሂደታቸው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝም ተጠቁሟል። ‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መሶብ አንድ ማዕከልአገልግሎት ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ አህመዲን አወል እንደገለጹት በክልሉ የመጀመሪያ የሆነው የሚዛን-አማን ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለሕብረተሰቡ ሰፊ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ‎በማዕከሉ አምስት የክልልና አራት የፌዴራል ተቋማት 35…

Read More

በራሳቸው ፋብሪካ እሴት ጨምሮ በመሸጥ ከሌሎች ጥገኝነት ለመላቀቅ እንደሚሰሩ በካፋ ዞን በሻይ ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ገለጹ።

አርሶ አደሮቹ በአሁኑ ሰዓት ያመረቱትን ሻይ ለውሽውሽ ሻይ ልማት ድርጅት እያቀረቡ መሆኑንም ጠቁመዋል። በዞኑ ጊምቦ ወረዳ ምቺቲ ቀበሌ በ1997 ዓመተ ምህረት በ6 አርሶአደሮችና በ6 ሄክታር ማሳ ላይ የተጀመረው የሻይ ልማት ዛሬ አድማሱን አስፍቶ በወረዳው 6 ቀበሌዎችን ከማዳረሱም በላይ በርካታ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል። ምርት መስጠት ባቆመ አሲዳማ መሬት ሊይ በመተከል ውጤት መስጠት የሚችል ከመሆኑም…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት አስጀመሩ

ዛሬ ስራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፣ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሰራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ስርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ ነው። ‎አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ስርዓት ያለው ሲሆን፣ የተለያዩ የክፍያ አማራጮችንም አካቷል።…

Read More

54ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብስባ ውሳኔዎች

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው ለአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ የሰማንያ ሚሊዮን (80,000,000) ዩሮ ብድር ስምምነት ነው፡፡ ሁለተኛው ለአነስተኛ የገጠር ገንዘብ አቅርቦት ማሻሻያ ፕሮግራም የሚውል ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት…

Read More

መገናኛ ብዙኃን የወል ትርክት ግንባታ ላይ በትኩረት እንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን መገናኛ ብዙኃን የሀገር ግንባታ ሂደትን ለማጠናከርና የወል ትርክትን ለመገንባት በትኩረት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርቧል። ባለስልጣኑ ከሚዲያ ተቋማት ከተውጣጡ ተወካዮች ጋር “መገናኛ ብዙኃን ለሀገር ግንባታ እና ለማህበረሰብ አመለካከት ቀረጻ” በሚል መሪ ሐሳብ ውይይት እያካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን መገናኛ ብዙኃን በሚሰሯቸው ስራዎች መሻሻሎች መኖራቸውን…

Read More

ከዕዳ ጥገኝነት ወደ ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት

ኢትዮጵያ ከአሳሪውና ከአባካኙ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ሥርዓት ወጥታ፣ በዕውቀትና በዲሲፕሊን የሚመራ ጠንካራ የኢኮኖሚ መዋቅር መገንባት ችላለች። የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሀገራዊ ጸጋዎችን ወደ ላቀ ምርታማነት ለመቀየርና የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባቶችን በዘላቂነት ለመፍታት የጀመራቸው ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ሥራዎች፣ ዛሬ ላይ ሀገራችንን በዓለም ፈጣን ዕድገት ካላቸው አሥር ሀገራት ተርታ እንድትሰለፍ አድርገዋታል። አሁን ላይ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በተለያዩ ውስብስብ ሀገራዊና…

Read More

ከክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 302 ነጥብ 27 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሄራዊ ባንክ ቀርቧል

በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 302 ነጥብ 27 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረቡን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ። ከክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ወልያብ (ዶ/ር) እንደገለጹት ኤጄንሲው በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት 262 ነጥብ 5 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ለማቅረብ…

Read More