BLOGS

አመራሩ የፓርቲ ሥራዎችን በላቀ ቁርጠኝነት እንዲመራና እንዲፈጽም አቶ ፍቅሬ አማን አሳሰቡ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በቴፒ ከተማ ሲያካሂድ የነበረው የ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተጠናቀቀ። በመድረኩ በዘጠኝ ወራት የተመዘገቡ የተሻለ አፈጻጸሞችን ማጠናከር እና ጉድለቶችን ማረም የሚያስችሉ ገንቢ ሀሳቦች ተነስተው የጋራ ውይይት ተደርጓል። በግምገማው ማጠቃለያ ላይ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን አመራሩ የፓርቲውን መደበኛና ኢንሼቲቭ…

Read More

ሪፖርታዥ

ሪፖርታዥ ላለፉት 9 ወራት የአርብቶ አደሩን ኑሮ የሚያሻሽሉ ውጤታማ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የአርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢ ጉዳይ ቢሮ ገለጸ በአርብቶ-አደር እና ከፊል አርብቶ አደር ማህበረሰብ አካባቢ ፈጣንና ፍትሐዊ ልማት ለማረጋገጥ  እንደ ሀገር የተነደፉ የፖሊሲ ማሻሻያዎችና ማስፈጸሚያ ስትራቴጂዎችን ከክልላችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማስተሳሰር በርካታ ማህበራዊና ኢኮኖሚዊ የልማት ስራዎች መሰራታቸውን ቢሮው ገልጸዋል፡፡ በአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ዘንድ የሚነሳውን…

Read More

የዓመቱን ስራ በላቀ ሁኔታ ለመጨረስ ያለመ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተጀመረ

በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም በቴፒ ከተማ እየገመገመ ይገኛል። የግምገማ መድረኩ ፓርቲው በ2018 በጀት ዓመት ያቀዳቸውን ግቦች በዘጠኝ ወራት ውስጥ ምን ያህል እንደፈጸመ በመፈተሽ፣ በቀሪዎቹ ወራት ለሚከናወኑ ተግባራት ግልጽ አቅጣጫ ለማስቀመጥ የታለመ ነው። በዚህም በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተከናወኑ ሥራዎችን በጥልቀት በመገምገም፣ የተመዘገቡ ጠንካራ ጎኖችን…

Read More

የእንስሳት ሀብት በተገቢው በማልማት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባ ተገለጸ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ የተገነባውን የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል መርቀው ከፍተዋል። በያዶታ ከተማ የተገነባው የቁም እንስሳት የግብይት ማዕከል በአከባቢው ያለውን የእንስሳት ሀብት በተገቢው ለመጠቀም የሚያግዝ መኾኑን ነው ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በምረቃው ወቅት የገለጹት። የማዕከሉ መገንባት በአከባቢው ያለውን እምቅ የእንስሳት ሀብት ዘመናዊ…

Read More

ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ከ353 ሚሊዮን ብር ለሚገነባው ሆስፒታል የመሠረተ ድንጋይ አስቀመጡ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፥ በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ፣ የያዶታ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግንባታ መሠረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል። ከ353 ሚሊዮን በላይ በሆነ የክልሉ መንግሥት የበጀት የሚገነባው የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአግልግሎት ክፍት እንደሚኾን ተመላክቷል። የሆስፒታሉ መገንባት ከዚህ ቀደም በአከባቢው ከጤና ተቋማት ተደራሽነትና ጥራት ጋር ተያይዞ…

Read More

የማኅበራዊ ልማት ሰጪ መሠረተ ልማት ለማስፋፋት ቅድሚያ ተሰጥተው እየተሰራ ይገኛል – ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፥ በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ፣የያዶታ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግንባታ መሠረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል። በስነስርዓቱ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ ባስተላለፉት መልዕክት የክልሉ መንግሥት የማኅበራዊ ልማት ሰጪ መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ቅድሚያ ተሰጥተው እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የብልፅግና ፓርቲ የዜጎችን ኑሮ በተጨባጭ ለመቀየር ይሰራል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ ከለውጡ በፊት ሰፊ የልማት…

Read More

የኢትዮጵያ ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ምኅዳር የቼክ ሪፐብሊክ ባለሃብቶችን ቀልብ እየሳቡ ነው

የኢትዮጵያ ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ምኅዳር የቼክ ሪፐብሊክ አልሚ ባለሃብቶችን ቀልብ እየሳቡ እንደሚገኝ የቼክ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ራዴክ ሩበሽ ገለጹ። የኢትዮጵያ እና ቼክ ሪፐብሊክ ታሪካዊ ግንኙነትም በሁሉም መስክ የትብብር አድማሱን እያሰፋ እንደሚገኝም ተናግረዋል። የኢትዮ-ቼክ ሪፐብሊክ የፖለቲካል ዲፕሎማቲክ ግንኙነት እ.አ.አ ከ1918 ጀምሮ በታሪካዊ ወዳጅነትና ትብብር እየጎለበተ መምጣቱን መረጃዎች ያመለክታሉ። የቼክ ሪፐብሊክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር…

Read More

በዳውሮ ዞን ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

በዳውሮ ዞን ያለውን አጠቃላይ የልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮችን ማዕከል ያደረገ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለጹት፤ ውይይቱ የዞኑን አሁናዊ ሁኔታ በጥንካሬና በድክመት በመፈተሽ አመራሩን ለቀጣይ ተልዕኮ ዝግጁ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል። በከተማና በገጠር የሚነሱ የሕዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በብቃት ለመመለስና ማህበራዊ…

Read More

‎የ2018 ዓ.ም የሸካ ዞን እግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና ዉድድር በቴፒ ከተማ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

‎ከሚያዝያ 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 8 ቀናት ሲካሄድ የቆየዉ የ2018 ዓ.ም የሸካ ዞን እግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና ዉድድር ፍፃሜውን አግኝቷል ። ‎በዉድድሩ መዝጊያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ስፖርት በስነ ምግባር የታነፀ፣ በአካል የዳበረ ፣በአዕምሮ የበለፀገ፣ በህብረ ብሄራዊ ኢትዮጵያዊነት የሚያምን ዜጋን ለመፍጠር ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ገልፀዉ ለዉድድሩ…

Read More

ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 50 ሚሊየን 514 ሺህ በላይ መራጮች ተመዝግበዋል፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ 50 ሚሊየን 514 ሺህ በላይ መራጮች መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገለጹ። የሰባተኛው ጠቅላላ የመራጮች ምዝገባ ትናንት ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ተጠናቋል። ዜጎች በምርጫዬ የሞባይል መተግበሪያ የዲጂታል አማራጭና በምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት የመራጮች ምዝገባ አከናውነዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የመራጮች ምዝገባ መጠናቀቅን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ፤ ቦርዱ…

Read More