ኢትዮጵያ በኮቪድ 19 ወረርሺኝ የተጎዳውን የቱሪዝም ዘርፍ በማነቃቃት ባለፉት 5 አመታት የአለም አቀፍ ጎብኚዎቿ ቁጥር በ40 በመቶ እድገት ማሳየቱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቱሪዝም ዘርፍ መረጃ አመልክቷል።

በዚህም እ.አ.አ ከ2019 ወዲህ ባስመዘገበችው የቱሪስት ፍሰት መጠን ኢትዮጵያ ከአለም ሃገራት ስድስተኛ እንዲሁም ከአፍሪካ ደግሞ ሞሮኮና ግብፅን በማስከተል ቀዳሚ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

Read More

” በዛሬው እለት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የተገነባውን የኢቲ ማዕድን ልማት አ.ማ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካን መርቀን ስራ አስጀምረናል። ፋብሪካው በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የድንጋይ ከሰል ምርት ከማሻሻል ባሻገር ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ እድል የፈጠረ ነው። “ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Read More