




ምክርቤቱ በሁለተኛው ቀን የ2017 ዓ/ም ተጨማሪ የበጀት ረቂቅን መርምሮ አጽድቋል።
የተጨማሪ በጀት ረቂቅ አዋጅ በ2017 በጀት ዓመት ለመንግስት ሰራተኞች የ9 ወራት የደመወዝ ማሻሻያ ክፍያ በጀት መሆኑን የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ አቅርበዋል።
የቀረበው ተጨማሪ በጀት ከክልል ጀምሮ እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን ወርዶ ተፈጻሚ እንደሚሆንም ተገልጿል።
በተጨማሪ የበጀት ረቂቅ አዋጅ 2 ቢሊዮን 247 ሚሊዮን 385 ሺህ 094.02 ብር ሆኖ የቀረበውን የምክርቤት አባላት በሙሉ ድምጽ በማጽደቅ ስራ ላይ እንዲውል ተደርጓል።
በታጠቅ አበበ
