ለሁለት ቀናት በቴፒ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የክልልና የዞን ምክር ቤቶች የጋራ የምክክር መድረክ ተጠናቋል

Spread the love

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዋና አፈ-ጉባኤ ክቡር አቶ ወንድሙ ኩርታ የምክር ቤቶች አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መጥተዋል ብለው የታዩ መልካም ተሞክሮዎችን በማስፋት በቀጣይም ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል ፡፡

የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ- ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፀሀይ ደርጫ በበኩላቸው የጋራ ምክክር መድረኩ በየደረጃው ያሉት ምክር ቤቶችን አቅም ለማጎልበት የሚረዱ ተሞክሮዎች የሚወሰዱበት መሆኑን ተናግረዋል።

በመጨረሻም ሞዴል አፈፃፀም ያሳዩ ምክር ቤቶችን በመሸለም መድረኩ ተቋጭቷል።

በተከተል ወ/ሚካኤል

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *