




በበጀት ዓመቱ ታቅደው በብልጽግና ቤተሰብ ደረጃ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን የተመለከተ ሪፖርት ህብረቱ ሰብሳቢ አቶ ሳምሶን መለሰ አቅርበዋል ።
የህብረቱ ሰብሳቢ ባቀረቡት ሪፖርት የብልጽግና ቤተሰብ በበጀት ዓመቱ ዕቅዳቸውን ውጤታማ እንዲያደርጉ ተገቢው የድጋፍና ክትትል ስራዎች መሰራታቸውን አብራርተዋል ።
ከክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚወርዱ ሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ይዘት ያሏቸውን ተልዕኮ ለመፈጸም እንዲያስችል የአባላት አቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው መሰራታቸውን አብራርተዋል ።
በህብረቱ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና በአፈጻጸም ሂደት የነበሩ ጉድለቶችን እንዲሁም የ2018 ዓ/ም ጠቋሚ ዕቅድ ቀርቦ አባላት መክረውበታል።
አባላት በበጀት ዓመቱ የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል የታዩ ደካማ አፈጻጸሞችን በመለየት በቀጣይ በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ መስራት አለብን ብለዋል።
በታጠቅ አበበ
