




ዘንድሮ ከ50 ዓመታት በኃላ ለ2ተኛ ጊዜ የሚከበረው የሸኮ ብሄር ዘመን መለወጫ እና ምስጋና በዓል “ቲከሻ ቤንጊ” በድምቀት ለማክበር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
በዓሉ በድምቀት እንዲከበር እንዲሁም ለትውልድ ለማስተላለፍ ሶስቱ ወረዳዎችና ሶስቱ ከተማ አስተዳደሮች በቅንጅት እና ትብብር መስራት ከጀመሩ ሰንብቷል።
ለዚሁም ተግባር ስኬታማነት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሪፖርት ባለድርሻ አካላት በተገኙት ተገምግሟል ።
በመድረኩ ክቡር አፈ ጉባኤ ወንድሙ ኩርታን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፎዋል።
የዘንድሮ የሸኮ ብሄር ዘመን መለወጫ እና ምስጋና በዓል ከጥር 8/2017ዓ/ም ጀምሮ ከቀበሌዎች ጀምሮ በድምቀት በመከበር ላይ እንደሚገኝ የሸኮ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
