‎ላለፉት 4 ዓመታት ለተጨማሪ 490 ሺህ ነዋሪዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ማድረስ እንደተቻለ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ገለፀ።

Spread the love

‎የቢሮ ሀላፊ የሆኑት ኢንጂነር በየነ በላቸው የንፁህ መጠጥ ውሃ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚጠይቅ በመሆኑ የተለያዩ አጋር አካላት ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠይቀዋል።

‎በክልሉ የንፁህ መጠጥ ውሃና ሌሎች መሰረት ልማት አነስተኛ እንደነበረ ነው ኢንጅነር በየነ በላቸው ከዝግጅት ክፍላችን ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት የገለፁት።

‎የክልሉ መንግስት ችግሩን ለመቅረፍ በወሰደው ልዩ እርምጃ በክልሉ የንፁህ መጠጥ ውሃና የሌሎች መሰረተ ልማት ተደራሽነት እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

‎ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ የውሃ ፕሮጀክቶች ለማጠናቅና በክልሉ መንግስት ልዩ በጀት ድጎማ የተለያዩ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ለመገንባት በተወሰደው ልዩ እርምጃ የተለያዩ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀው አገልግሎት እየሰጡ እንደሆነ ጠቁመዋ

‎የተለያዩ የውሃ ፕሮጀክቶች መመረቅ የክልሉን የውሃ ሽፋንና የተጠቃሚዎችን ቁጥር እያሳደገ ይገኛል ብለዋል።ክልሉ ላለፉት 4 ዓመታት በሰራው ስራ ተጨማሪ 490 ሺህ ነዋሪዎችን የንፁህ መጠጥ ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ ገልፀው የተደራሽነት ሽፋኑን ወደ 43% ማድረስ ተችሏል ብለዋል።

‎በክልሉ በቦንጋ፣ ሚዛንና ሌሎች ትላልቅ ከተሞች ከነዋሪዎች ቁጥር መጨመር ጋር ተያይዞ የውሃ እጥረት እንደምታየው የገለፁት ሀላፊው ለችግሮቹ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ጥናቶች ተጠናቆ ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።

‎በንፁህ መጠጥ ውሃና በሌሎች መሰረ ልማት ግንባታዎች የህብረተሰብ ተሳትፎ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ በመምጣቱ ምስጋናቸውን አቅርበው አሁንም ለጋራ ተጠቃሚነት እጅ ለእጅ ተያይዞ መስራት እንደሚገባ ጠይቀዋል።

‎የንፁህ መጠጥ ውሃ ግንባታ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እንደሚጠየቅ ያብራሩት ሀላፊው የተለያዩ አጋር አካላት ለንፁህ መጠጥ ውሃ ግንባታ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክሮ እንድያስቀጥሉ ጠቁመዋል።

‎በንጉሴ ወልደየስ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *