ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) የፍትህና የአስተዳደር ጉዳዮች አፈጻጸምን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል

Spread the love

👉ከአንጻራዊነት ወደ ዘላቂነት እየተሸጋገረ ያለውን የክልሉን ሠላም ለማጽናት 225,174 የህብረተሰብ ክፍሎችን በሰላም፣ በብዝሃነት፣ በአብሮነትና በሰላም ግንባታ ዙሪያ ግንዛቤ በመፍጠር የአካባቢያቸውን ደህንነት በመጠበቅ ሰላምን በማረጋገጥ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማድረግ ሥራ ተሰርቷል፤

👉 58 የሰላም ምክር ቤቶችን በማጠናከር ወደ ስራ ማስገባት ተችሏል፤

👉በሁሉም የወንጀል አይነቶች 4,081 መዝገቦች በዐቃቤያነ ህግ አስተያየት እና ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል፤

👉በኮሚሽኑ በመታረም ላይ ለሚገኙ 1340 ታራሚዎች ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል የቀለም ትምህርት እንዲያገኙ ተድርጓል፤

👉በሚዲያ መግለጫዎችም መንግስታዊ ሥራዎችን ለህዝብ ማድረስ በፕሬስ ሪሊዝም በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች የመንግስትን አቋም የማሳወቅ ሥራዎች ተከናዉኗል፣

👉የተለያዩ ሀገራዊና ክልላዊ ሚዲያዎችን በማስተባበርም ሰፊ የልማት ሥራዎች ከህዝቡ ጆሮና ዓይን እንዲገቡ በስፋት ተሰርቷል፤

👉የሚዲያና የህዝብ ግንኙነቱን ሥራ በአጀንዳ በመምራት፣ ብሔራዊና ክልላዊ ሁነቶች በታቀደላቸው መሠረት እንዲመሩ ተደርጓል።

👉የሪፎርም ሥራዎች ትግበራን ከማጠናከር አኳያ፤ በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ዝግጅት ምዕራፍ ትግበራ ሰነድ በ 10 የፖሊሲ ማስፈጸሚያ ስትራቴጂዎች እና የፍኖቴ ካርታን ክልላዊ ይዘት ጠብቆ 1 ዙር ለማዘጋጀት ታቀዶ 1(100%) ተዘጋጅቷል።

👉በሰዉ ሃብት አመራር ልማት ዘርፍ ከመገንባት እና ከማብቃት አኳያ፤ የሰራተኞች ክልላዊ የሥራ መደብ ለማሻሻል 6806 ታቅዶ 3873 (57%) መታወቂያ ቁጥር ተሻሽሏል።

👉በአስቸኳይ ሙስና መከላከል ስራ ሊመዘበር የነበረ እና በኦዲት ግኝት ክትትል ተደርጎ ብር 47,560,300 ማስመለስ ተችሏል፡፡ 1404 አዲስ የሀብት ምዝገባና ትክክለኛ ማረጋገጫ ማካሄድ ተችሏል፡፡

በፍቅር ከበደ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *