የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ በአቶ በላይ ተሰማ የተመራ የድጋፍና ሱፐርቪዥን ቡድን በሸካ ዞን ያደረገዉን የመስክ ምልከታ አስመልክቶ በቴፒ ከተማ ገምግሟል።

Spread the love

በዞኑ በአስራ አንድ ወራት የተከናወኑ የፓሪቲ ተግባራት አፈፃፀም ሪፖርት ለሱፐርቪዥን ቡድኑ ገለፃ ተደርጓል።

በአንድራቻ ወረዳ በዮኪ ጭጭ እና ገማድሮ ቀበሌዎች በህዋስና መሠረታዊ ድርጅት የመረጃ አያያዝ ስርዓቱ የተሻለ መሆን ንዑሳን ኮሚቴዎችን ለይቶ ወደ ስራ ከማስገባት ከእዳ ወደ ምንዳ ስልጠና የተሠጠበት መንገድና ወደ መሬት ከማዉረድ አንፃር የተሠሩ ተግባራት አበርታች መሆናቸዉ ተገምግሟል።

በሌማት ትሩፋት ስራዎች በተለይም በዶሮ እርባታ፣ በእንስሳት ተዋጽኦ፣ በማር ምርት እና በዓሳ ሀብት ልማት ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ ስለመሆናቸው ተብራርቷል ።

በስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ወጣቶችን በማደራጀት የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻልም እየተሰራ ያሉ ስራዎች አበረታች ብሆኑም በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች የብድር አገልግሎት አለመመቻቸት እና የቦታ ጥቤት እንደ ችግር የተነሱ ናቸዉ።

የሴቶችንና የወጣቶችን አቅም በማሳደግ የመሪነት ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ስራ መሰራት እንዳለበት ተጠቁሟል።

በህብረተሰብ ተሳትፎ አንጻር በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች እንዲሁም በጸጥታው ዘርፍ በሁሉም መዋቅሮች የተሻሉ ስራዎች በመኖራቸው ይህንን አጠናክሮ በማስቀጠል የህዝብ ተጠቃሚነት እንድረጋገጥ መስራት እንደሚያስፈልግም ተጠቁሟል።

አመራሮችን ከማደራጀትና ከማጠናከር፣ የንቅናቄ አጀንዳዎችን ከማከናወን፣ ከብድር አመላለስ ፣የጤና መድን ሽፋንን ከማስፋት፣ ከተፎካካሪ ፓሪቲዎች የጋራ ምክር ቤት ማቋቋም እንደተቻለ፣ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ የልማት ተግባራት በዞኑ እየተከናወኑ ስለመሆናቸዉ ተገምግሟል።

የበጋ ስንዴ ውጤታማነት፣ የሌማት ትሩፋቶች እና አጠቃላይ በሁሉም የማህበራዊ መሰረቶች በፓርቲው መሪነት የተሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የተሻሉ መሆናቸውንና ይህንን በለሎች ዘርፎች አጠናክሮ ለማስቀጠል ቅንጅታዊ አሰራር ይሻል ተብሏል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይ ተሰማ በዞኑ እየተከናወኑ ያሉ የፓሪቲና የልማት ስራዎች አበረታች መሆናቸዉን ገልፀዉ ይህም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

አክለዉም የፓርቲውን ተቋማዊ አቅም የሚያጠናክር ቀጣይነት ያላቸው የአመራርና የአባላት አስተሳሰብ፣ የተግባር አንድነትና አፈፃፀምን መሰረት በማድረግ የአቅም ግንባታ ስራዎችን መስራት እንደሚገባ አሳስበዉ በሠላም ዕሴት ግንባታ ላይ በክረምት በጎ አገልግሎት በጤናዉ እና በለሎች ዘርፎች ጠንክሮ መስራት ይገባል ብለዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *