የክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ከመጋቢት 08/2018 ጀምሮ በቴፒ ከተማ እንደሚያካሂድ አስታወቀ

Spread the love

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 4ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቴፒ ከተማ ላይ እንደሚያካሄድ የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ጌታቸው ኬኒ ገልፀዋል።

በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ፀጥታን ፣ የዝርፊያና የስርቆት ወንጀሎችን መከላከል እንዲሁም ከወሰን ጉዳዮች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲፈቱ የማድረግ ስራዎች ላይ ምክር ቤቱ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

ነገ በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ በ2018 ዓ.ም 6 ወራት ውስጥ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ቀርቦ ውይይቶች እንደሚደረጉ ዋና አፈጉባኤው በመግለጫቸው ጠቁመዋል።

በጉባኤው ላይ የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ የሁሉም ብሔረሰብ ተወካዮች እና የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ምክር ቤቱ አስታውቋል ሲል ማሻ ኤፍ ኤም ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *