






የለውጡ ትሩፋቶችን የሚዘክር ታላቅ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በቦንጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
የድጋፍ ሰልፍ በለውጡ መንግሥት የተገኙ የመጋቢት 24 ድሎችንና ሁለንተናዊ ለውጦችን የሚዘክር እንዲሁም ለተገኘው ለውጦች እውቅናን የሚሰጥ ነው።
የድጋፍ ሰልፋ በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የብልጽግና ፓርቲ መሪነት የተመዘገቡ ለውጦችን የሚገልጹ የተለያዩ መልዕክቶች በሰልፈኞቹ እየተላለፈ ነው።
ነዋሪዎቹ በለውጡ መንግሥት እየተከናወኑ ላሉ የልማት ሥራዎች እውቅና በመስጠት ፣ በቀጣይም የተገኘው ልማት እንዲቀጥል ከለውጡ ከመንግሥት ጎን መኾናቸውንም ገልጸዋል።
