ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የኦሮምያ ክልል ርዕሰመስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ጋር በአምቦ ወረዳ በነበራቸው ጉብኝት የኬኛ ቤቭሬጅ ፋብሪካን ተመልክተዋል። ፋብሪካው በመጪዎቹ ሶስት ሳምንታት ውስጥ ወደሥራ የሚገባ ሲሆን 3 ሚሊዮን ሄክቶሊትር የማምረት አቅምም አለው።

Spread the love

የአስተዳደር ሥራን ወደ ሕዝብ ለማቅረብ የቀበሌዎች መጠናከር ወሳኝ ነው። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በየአካባቢው ለሕዝብ ቅርብ የሆነ አስተዳደር ለመፍጠር (power devolution) ጥረት እያደረገ ነው። ከዚህ አንጻር በአምቦ ወረዳ የአንድ ቀበሌ እንቅስቃሴ በጉብኝት ወቅት ታይቷል። በዚህ ቀበሌን የማብቃት ተግባር በክልሉ 7342 ቀበሌዎች ተደራጅተዋል። 50,000 የሰው ኃይል ተመድቦላቸዋል።

ከዚህ ቀደም በወረዳዎች ተማክለው የነበሩ ሞያዊና አስተዳደራዊ አገልግሎቶች በቀበሌ ደረጃ በተገቢው የሰው ኃይል እየተሰጡ ይገኛሉ።

ከዚህ በተጨማሪ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የወንጪ ደንዲ ኤኮ ሎጅ አካል የሆነው የደንዲ ክፍል ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተዋል። የሥራው የሲቪል ግንባታ ሥራዎች ምዕራፍ ተጠናቆ አሁን የማጠናቀቂያ ሥራዎች በመሠራት ላይ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *