በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሁሉም ዞኖች የ2017 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአጠቃላይ አመራር አካላት ግምገማ እና ምዘና መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

Spread the love

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሁሉም ዞኖች የ2017 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአጠቃላይ አመራር አካላት ግምገማ እና ምዘና መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በዞኖች የተጀመረው የአጠቃላይ አመራር አካላት ግምገማ እና ምዘና በአመለካከት፣ በስነምግባር፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ፤በተግባር አፈጻጸምና ዉጤታማነት ላይ ዓላማ ያደረገ መድረክ ነዉ።

ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት በሀገሪቱ የተለያዩ ፈታኝ ሁኔታዎችን እያለፈ ዘርፈ ብዙ ስኬቶችን እያስመዘገበ የሚገኘውን ውጤት ቀጣይ ለማድረግ አመራሩ ግንባር ቀደም ሚና እንዲወጣ ወቅታዊ የግምገማ እና ምዘና መድረኮች ወሳኝነት እንዳላቸውም ተመላክቷል።

የግምገማና ምዘና ስርዓት ዋና ዓላማው ሁለንተናዊ ብልጽግና የማረጋገጥ ራዕይን እውን የማድረግ ዓላማን ያነገበ ሲሆን ይህም የአመለካከት ጥራት፣የታነፀ ስነ ምግባር የተላበሰ፣ በእውቀት እና በአፈፃፀም የበቁ እና የላቁ አመራርን ለመፍጠር ምቹ መደላድል እንደሚፈጥርም ተጠቅሷል።

ምዘናው በአፈጻጸም ወቅት የሚታዩ ችግሮችን የሚፈታ ፣የመፍትሔ አቅጣጫ የሚያስቀምጥ ፣በየአካባቢው ያሉትን የህዝቡን የልማት፣ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ሊያጎላ የሚችል እርስ በእርስ የመገነባቢያ መድረክ ጭምር ነዉ።

በፍቅር ከበደ

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇

📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/

📌በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et

📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications

📌በትዊተር twitter.com/sweprs

📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi

📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab

📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

📌በዋትስአፕ

https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x

📌https://www.linkedin4v .com/company/southwest-communications/

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *