


የመግባቢያ ሰምምነቱን የተፈራረሙት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እና የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ ናቸው።
የመግባቢያ ስምምነቱ ለሚኒስቴሩ ራዕይ ስኬታማነት ለፕሮጀክቶች ቴክኒካል ድጋፍና ክትትል ለማድረግ እንዲሁም የአፈጻጸም አቅምን ማጎልበት ዓላማ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
በጨርቃ ጨርቅ፣ በእርሻ ውጤቶች፣በቆዳ፣ በኬሚካል እና ኮንስትራክሽን፣ በቴክኖሎጂ፣ በፋርማሲ ውጤቶች የስራ ዕድል መፍጠር የስምምነቱ አንድ አካል ነው።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እ.አ.አ በ2030 ኢትዮጵያን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንድትሆን የማስቻል ራዕይ አንግቦ እየሰራ እንደሚገኝ ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
