ወጣቶች የሀገራቸውን የወደፊት ዕጣ ፋንታ የማሳመር ሂደት ላይ ሊሳተፉ ይገባል ተባለ




የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ወጣቶች ሀገሪቱ ያለፈችባቸውን መንገዶች የማስተካከል ብቻ ሳይሆን መጪውን እጣ ፋንታዋን የማሳመር ሂደት ላይ ንቁ ተሳታፊ ሊሆኑ ይገባል አለ።
ምክክር ኮሚሽኑ ‘የወጣቶች ሚና ለውጤታማ ሀገራዊ ምክክር’ በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከአማራ ክልል ወጣቶች ጋር የሚያካሂደውን ውይይት የመጀመሪያው ምዕራፍ ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ ጀምሯል።
በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር ብሌን ገብረ መድኅን እንዳሉት፤ ወጣቶች ኢትዮጵያ ያለፈችባቸውን መንገዶች የማስተካከል እና መጪውን እጣ ፋንታዋን የማሳመር ሂደት ላይ በንቃት መሳተፍ አለባቸው።
ከአሁን በፊት በነበሩ የምክክር ኮሚሽኑ ሂደቶች ወጣቶችን እንደ አንድ የማኅበረሰብ ክፍል መሳተፋቸውን አስታውሰዋል።
ይህንን ተሳትፎ ለማጠናከርም የተለያዩ የሃሳብ ግብአቶችን ለማግኘት ከተለያዩ ሙያዎች የተውጣጡ ወጣቶችን ማሳተፍ ማስፈለጉንም ተናግረዋል።
ከአማራ ክልል ወጣቶች ጋር የሚያካሂደው የመጀመሪያ ምዕራፍ ውይይት ለአራት ቀናት ይቆያል።
በመድረኩም በሀገራዊ ምክክር ሂደት የወጣቶች ተሳትፎና ሚና፣ በምክክሩ ሂደት የወጣቶች ትርጉም ያለው ተሳትፎና አካታችነት እንዲጎለብት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሚና ተግባራት እና ሌሎች ሃሳቦች ላይ ውይይት ይደረጋል ሲል ኤፍኤም ሲ ዘግቧል።
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን ![]()
በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
በትዊተር twitter.com/sweprs
በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication
በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
በሊንክደን
