ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የዜጎችን ሁለንተናዊ ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ ሁሉም የህብረተሰቡ ክፍል የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል በቁርጠኝነት መስራት ይገባል ፦ አቶ ፍቅሬ አማን

Spread the love

‎በፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሂደት የእስካሁኑ አፈጻጸም ፣ በተግዳሮቶች መፍትሔ መንገድና በቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

‎የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ “የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ያልተናነሰ ብሔራዊ ጥቅም እንዳለው ገልጸውታል ሲሉ ተናግረዋል።

‎ፋይዳ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን ከሃገራዊ ትልሞቻችን ጋር ተናባቢ ዕሳቤ እንዳለውና ይሄንንም ትልም ዕውን ለማድረግ ሀሉም ባለድርሻ አካላት በሙሉ አቅም መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

‎ፋይዳ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ዕድገትና ለዘመነ አገልግሎት አሰጣጥ አስቻይ ከሆኑ መሰረቶች ውስጥ ዋነኛው መሆኑን የገለጹት አቶ ፍቅሬ በምዝገባ ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በፍጥነት በማረም የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት በቅንጅት መረባረብ ይገባል ተብለዋል።

‎የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይ ተሰማ እንደ ክልል የተያዘውን የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መተወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ ተግባራዊ ለማድረግ ከወዲሁ በቁርጠኝነት መስራት ይገባል ያሉ ሲሆን በየአካባቢው የተሰሩ ስራዎችን በጥንካሬና በድክመት አብራርተዋል።

‎እስካሁን በተግባር አፈጻጸም ሂደት ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች በፍጥነት በማረም የተቀመጠውን ክልላዊ ግብ ለማሳካት በልዩ ትኩረት መከወን እንደሚገባ ጠቅዋል።

በመድረኩ የኢትዮ ቴሌኮም አመራሮች ፣የዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች ፣የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *